https://m.facebook.com/gracet.sewoch?ref_component=mbasic_home_header&ref_page=%2Fwap%2Fhome.php&refid=7
በአገሪቱ ውስጥ የተፈጠረውን ተቃውሞ ተከትሎ ስለ ሰላም በቁንፅል ትርጉም እየሰጡ ረጂም ዲስኩራቸውን እያሰሙ ነው፡፡ እዚህ ውስጥ ፊደል ከቆጠሩ አንስቶ ጌቶቹ የሰጡትን ሳያላምጥ እስከሚውጠው ካድሬ ድረስ ልፈፋቸው ተመሳሳይ ነው፡፡ ሌላው አስገራሚ ነገር ደግሞ የሰላም ተመራማሪ ነን የሚሉ የአገዛዙ የስጋ ዘመዶች ለሰላም የሚሰጡት ትርጉም ተመሳሳይ መሆኑ ነው፡፡ ለነሱ ሰላም ማለት ጦርነት የሌለበት ሁኔታ ነው፡፡ ለዚህ ቁንፅል ትንተናቸው ሲሉ የሚያቀርቡት ማስፈራሪያ አይነት ምሳሌ ሶሪያንና ሊቢያን አታዩም ወይ የሚል ነው፡፡
ለግልብ ትንተናቸው ማሳያነት ሶሪያንና ሊቢያን ያንሱ እንጂ የአላሳድንም ሆነ የጋዳፊን ፈላጭ ቆራጭነት እንዲሁም በአገሪቱ ውስጥ ለተነሱ የለውጥ እንቅስቃሴዎች በዋነኝነት ተገቢውን መልስ መስጠት ባለመቻላቸው በግልፅ ቋንቋ ስልጣን ወይም ሞት ባሉ የአገዛዝ ቆሞ ቀሮች ግትርነት የመጣ ግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት እንደሆነ ደፍረው አይነግሩንም፡፡ ለምሳሌ የሁለቱን አገራት ሁኔታ በቅርብ የሚከታተሉ ተንታኞች በሶሪያም ሆነ በሊቢያ ከፀደዩ አብዮቱ በፊት የነበረው ሁኔታ ተመሳሳይ እንደሆነ ቢገልፁም ከአብዮቱ በኋላ የአገዛዙን ተፈጥሮአዊ ሁኔታ፣አለም አቀፍ ተፅእኖ፣በውስጥ ያለውን ሁኔታ፣ወታደራዊ እንቅስቃሴውን በማንሳት የሁለቱን አገሮች ሁኔታ አንድ አድርጎ ከመግለፅ ይልቅ ለያይተው ነው የሚያቀርቡት፡፡ የምሁርነት ካባ ያጠለቁ የኢህአዴግ የስጋ ዘመዶች ዋነኛ ጭንቀታቸው አገዛዙን በስልጣን ማቆየት በመሆኑ የሁለቱን አገራት ሁኔታ ለያይተው ሊያቀርቡ ቀርቶ የተረዱም አይመስልም።የወደፊቱን ሁኔታ የከፋ የሚያደርጉትም እንዲህ አይነቶቹ ናቸው፡፡
ሰላም የሚሉትም ጦርነት አለመኖሩንና ህዝቡ በፖሊስና በጦር ሃይል ተሰንጎ ተይዞ ጭጭ ብሎ በደሉንና ጥቃቱን ችሎ መገዛቱን ነው፡፡ ለማንኛውም ‹‹ጸጥ፣ለጥ ብሎ መገዛት ሰላም አይደልም፡፡›› በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በቁንፅል የመልካም አስተዳደር ችግር ያውም የአገልግሎት አሰጣጥ አድርጎ በመተርጎም እንዲሁም በአገዛዙ ውስጥ ያሉ ሰዎች ስልጣን አላግባብ መጠቀማቸው ብቻ ነው የችግሩ ምንጭ ለዚህም እንታደሳለን ማለት ፌዝ ነው። ከዚህም ከፍ ሲል ሊብያንና ሶሪያን ትሆናላችሁ ብሎ ማስፈራራት እንደ ከዚህ ቀደሙ በማምታታት ጊዜን መግዛት ይቻል ይሆናል እንጂ የለውጥ ኃይሉን ማቆም ይቻላል ማለት ዘበት ነው፡፡
ሰሞኑን በተደጋጋሚ እንደተመለከትነው በቴሌቭዢን መስኮት እየቀረቡ እንታደሳለን የሚሉትን ነባር ነጠላ ዜማ አምኖ የሚቀበል የለም፡፡ ከአስር አመት በፊት በስመ ተሃድሶ የግለሰብ ፈላጭ ቆራጭነት ገኖ የወጣበት ነበር፡፡ አሁንም ተሃድሶ እናደርጋለን ሲሉን መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት ሳይሆን ትናንሽ አሳዎችን በማጥመድ በሙስና ላይ ዘመትን በማለት እንዲሁም በተለያዩ የአገሪቱ አከባቢዎች በንፁሃን ደም የጨቀዩ፣ በሙስና የተዘፈቁ አመራሮችን ከክልል አንስተው ወደ ፌደራል፣ከፌደራል አንስተው ወደ ክልል በማዘዋወር ጊዜን ለመግዛት ነው። ስልጣን ወይም ሞት ያለ የአገዛዝ ስርዐት ከዚህ ተሻግሮ መሄድ አይችልም።
የለውጥ ጠያቂዎች ደግሞ አገዛዙን ሁለትና ሶስት እጥፍ አልፈው የሄዱ ናቸው። እንዲሁ በአፋዊ እንታደሳለን በሚል ማሞኛ አልያም ሶሪያን ትሆናላችሁ እና መሰል ማስፈራሪያ አያቆመውም። መሰረታዊ ለውጥን ልክ እንደመሬት ፖሊሲው በመቃብራችን ላይ ነው ካሉ ለውጥ ተፈጥሯዊ ነውና በዛ መንገድ ይዳኛሉ። ለማንኛውም ፓርቲ ይመጣል፣ ፓርቲ ይሄዳል። አገርና ህዝብ ግን ይቀጥላሉ። ኢትዮጵያ ከኢህአዴግ ዘመን በፊትም ነበረች ከኢህአዴግ በሁዋላም ትኖራለች።
ጉዞ ከአገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ→
በአገሪቱ ውስጥ የተፈጠረውን ተቃውሞ ተከትሎ ስለ ሰላም በቁንፅል ትርጉም እየሰጡ ረጂም ዲስኩራቸውን እያሰሙ ነው፡፡ እዚህ ውስጥ ፊደል ከቆጠሩ አንስቶ ጌቶቹ የሰጡትን ሳያላምጥ እስከሚውጠው ካድሬ ድረስ ልፈፋቸው ተመሳሳይ ነው፡፡ ሌላው አስገራሚ ነገር ደግሞ የሰላም ተመራማሪ ነን የሚሉ የአገዛዙ የስጋ ዘመዶች ለሰላም የሚሰጡት ትርጉም ተመሳሳይ መሆኑ ነው፡፡ ለነሱ ሰላም ማለት ጦርነት የሌለበት ሁኔታ ነው፡፡ ለዚህ ቁንፅል ትንተናቸው ሲሉ የሚያቀርቡት ማስፈራሪያ አይነት ምሳሌ ሶሪያንና ሊቢያን አታዩም ወይ የሚል ነው፡፡
ለግልብ ትንተናቸው ማሳያነት ሶሪያንና ሊቢያን ያንሱ እንጂ የአላሳድንም ሆነ የጋዳፊን ፈላጭ ቆራጭነት እንዲሁም በአገሪቱ ውስጥ ለተነሱ የለውጥ እንቅስቃሴዎች በዋነኝነት ተገቢውን መልስ መስጠት ባለመቻላቸው በግልፅ ቋንቋ ስልጣን ወይም ሞት ባሉ የአገዛዝ ቆሞ ቀሮች ግትርነት የመጣ ግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት እንደሆነ ደፍረው አይነግሩንም፡፡ ለምሳሌ የሁለቱን አገራት ሁኔታ በቅርብ የሚከታተሉ ተንታኞች በሶሪያም ሆነ በሊቢያ ከፀደዩ አብዮቱ በፊት የነበረው ሁኔታ ተመሳሳይ እንደሆነ ቢገልፁም ከአብዮቱ በኋላ የአገዛዙን ተፈጥሮአዊ ሁኔታ፣አለም አቀፍ ተፅእኖ፣በውስጥ ያለውን ሁኔታ፣ወታደራዊ እንቅስቃሴውን በማንሳት የሁለቱን አገሮች ሁኔታ አንድ አድርጎ ከመግለፅ ይልቅ ለያይተው ነው የሚያቀርቡት፡፡ የምሁርነት ካባ ያጠለቁ የኢህአዴግ የስጋ ዘመዶች ዋነኛ ጭንቀታቸው አገዛዙን በስልጣን ማቆየት በመሆኑ የሁለቱን አገራት ሁኔታ ለያይተው ሊያቀርቡ ቀርቶ የተረዱም አይመስልም።የወደፊቱን ሁኔታ የከፋ የሚያደርጉትም እንዲህ አይነቶቹ ናቸው፡፡
ሰላም የሚሉትም ጦርነት አለመኖሩንና ህዝቡ በፖሊስና በጦር ሃይል ተሰንጎ ተይዞ ጭጭ ብሎ በደሉንና ጥቃቱን ችሎ መገዛቱን ነው፡፡ ለማንኛውም ‹‹ጸጥ፣ለጥ ብሎ መገዛት ሰላም አይደልም፡፡›› በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በቁንፅል የመልካም አስተዳደር ችግር ያውም የአገልግሎት አሰጣጥ አድርጎ በመተርጎም እንዲሁም በአገዛዙ ውስጥ ያሉ ሰዎች ስልጣን አላግባብ መጠቀማቸው ብቻ ነው የችግሩ ምንጭ ለዚህም እንታደሳለን ማለት ፌዝ ነው። ከዚህም ከፍ ሲል ሊብያንና ሶሪያን ትሆናላችሁ ብሎ ማስፈራራት እንደ ከዚህ ቀደሙ በማምታታት ጊዜን መግዛት ይቻል ይሆናል እንጂ የለውጥ ኃይሉን ማቆም ይቻላል ማለት ዘበት ነው፡፡
ሰሞኑን በተደጋጋሚ እንደተመለከትነው በቴሌቭዢን መስኮት እየቀረቡ እንታደሳለን የሚሉትን ነባር ነጠላ ዜማ አምኖ የሚቀበል የለም፡፡ ከአስር አመት በፊት በስመ ተሃድሶ የግለሰብ ፈላጭ ቆራጭነት ገኖ የወጣበት ነበር፡፡ አሁንም ተሃድሶ እናደርጋለን ሲሉን መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት ሳይሆን ትናንሽ አሳዎችን በማጥመድ በሙስና ላይ ዘመትን በማለት እንዲሁም በተለያዩ የአገሪቱ አከባቢዎች በንፁሃን ደም የጨቀዩ፣ በሙስና የተዘፈቁ አመራሮችን ከክልል አንስተው ወደ ፌደራል፣ከፌደራል አንስተው ወደ ክልል በማዘዋወር ጊዜን ለመግዛት ነው። ስልጣን ወይም ሞት ያለ የአገዛዝ ስርዐት ከዚህ ተሻግሮ መሄድ አይችልም።
የለውጥ ጠያቂዎች ደግሞ አገዛዙን ሁለትና ሶስት እጥፍ አልፈው የሄዱ ናቸው። እንዲሁ በአፋዊ እንታደሳለን በሚል ማሞኛ አልያም ሶሪያን ትሆናላችሁ እና መሰል ማስፈራሪያ አያቆመውም። መሰረታዊ ለውጥን ልክ እንደመሬት ፖሊሲው በመቃብራችን ላይ ነው ካሉ ለውጥ ተፈጥሯዊ ነውና በዛ መንገድ ይዳኛሉ። ለማንኛውም ፓርቲ ይመጣል፣ ፓርቲ ይሄዳል። አገርና ህዝብ ግን ይቀጥላሉ። ኢትዮጵያ ከኢህአዴግ ዘመን በፊትም ነበረች ከኢህአዴግ በሁዋላም ትኖራለች።
ጉዞ ከአገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ→
No comments:
Post a Comment